ታሪኮች ስለ አማርኛ
የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ እንዴት ነውጥ ቀሰቀሰ (ክፍል አንድ)
የኢትዮጵያዊው አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ ኢትዮጵያ በብሔር እና ሃይማኖት ሥም የተፈፀሙ ነውጦች እና ሁከቶችን ለመጋፈጥ ተዳርጋለች።
ማንነትን መነሻ ያደረጉ ግጭቶች የኢትዮጵያን የማህበራዊ ሚዲያ የሐሳብ ልዉዉጥ እንዴት ሊያጋግሉ እንደሚችል
ከተለያዩ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ መሪዎች በታላቁ የኢትዮጵያ ቤተ-መንግስት ውስጥ የተሰራውን የአንድነት ፓርክ ምረቃ ስነ-ስርዓት ለማክበር በጥቅምት ወር 2012 ዓ.ም የሀገሪቷ ዋና ከተማ በሆነችው አዲስ አበባ ተገኝተው ነበር።
በኢትዮጵያ የመረጃ-ማዛባት ወረርሽኝ ውስጥ እየፈረሰ ያለው የገዢው ግንባር ዋነኛ ተዋናይ ነው
የቡድን ግጭት በጥቅምት ወር ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከተከሰተ በኋላ፣ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ደግሞ 'ማነው ተጠያቂው' የሚለውን ለመወሰን የነውጥ ትንታኔ እሰጣገባ ተጧጡፎ ቀጥሏል።
ኢትዮጵያውያኖች የብሔራዊ ቴሌቪዥናቸውን ‹ውሸቶች› በኤፕሪል ዘ ፉል ቀን አፌዙበት
ኢትዮጵያውያኖች የማሞኛ (አፕሪል ዘ ፉል) ቀንን በትዊተር ላይ በመንግሥት በሚተዳደረው የአገር ውስጥ ብቸኛ የቴሌቭዥን ጣቢያቸው (ኢቴቪ) ባስመሰሏቸው የውሸት አርዕስተ ዜኛዎች እንደንፁህ የወንዝ ወራጅ ውሃ በሚንኮለኮል ትዊቶች አጥለቅልቀውት እየተሳለቁ ቀኑን አክብረዋል፡፡
የ2013ቱን የአፍሪካ አገራት ዋንጫ ኢትዮጵያውያን በተለያየ ባንዲራ ውልብልቢት እያደመቁት ነው
በመላው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከባለፈው ዓመት የ2012 የአፍሪካ አገራት ዋንጫ ሻምፒዮን ጋር በኔልስፕሩት፣ ደቡብአፍሪካ ያደረገውን ከባድ ግጥሚያ በድምቀት እያከበሩ ነው፡፡ ከኢትዮጵያውያኑ ውብ አጨዋወት እና ከረዥም ጊዜ መጥፋት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ከታየው ድንቅ የተጫዋቾች ችሎታ ባሻገር፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከኳሱ ጎንለጎን ማዕከላዊ የውይይት አጀንዳ ለመሆን በቅቶ ነበር፡፡ በስታዲየሙ ጨዋታውን ለመመልከት የገቡት ኢትዮጵያውያን የተለያዩ ጽሑፎችን እና ባንዲራዎችን ሲያውለበልቡ ታይተዋል፡፡
የ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ይከበር›› እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ
በአዲስ አበባ የሚገኙ ወጣት ጦማሪ እና አራማጆች ከኢትዮጵያ የድርዜጎች (netizens) ጋር በማበር መንግሥታቸው የኢትዮጵያን ሕገ-መንግሥት እንዲያከብር ጠየቁ፡፡ ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ይከበር›› የተሰኘው እንቅስቃሴ በትዊተር እና በፌስቡክ ላይ የተካሄደው የኢትዮጵያ መንግሥት ሕገ-መንግሥቱን የጣሰባቸውን መረጃዎች በመለዋወጥ ነበር፡፡
‘ለሙሰኛ ባለስልጣን ምንም ምሕረት የለም’
የጨፌ ኦሮሚያ የዜና ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር እንዳስታወቁት አቶ አባዱላ ገመዳ ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው የሰመረ ግንኙነት ከተበላሸ (ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው ዝቅ ካለ) በኋላ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርሳቸው ሥም፣ በቤተሰቦቻቸውና በወዳጅ ዘመዶቻቸው አካባቢ ያከማቹትን ሃብት በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነትና በንብረት በታማኝ የኦህዴድ ፓርቲ አባላትና በደህንነት ሠራተኞች ሲሰባሰብ ነበር፡፡ . . .”
ኢትዮጵያ፤ ኢትዮጵያውያን የቡድናቸውን ማሸነፍ በጉጉት እየተጠባበቁ ነው
ምንም እንኳን የእግርኳስ ውጤት በአብዛኛው በጨዋታዎች እለት በሚፈጠሩ ክስተቶች ላይ ጥገኛ ቢሆንም ታሪክ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ያደላል። የሱዳን ብሄራዊ ቡድን ከሜዳው ውጪ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጋር ባደረጋቸው ያለፉት ዘጠኝ ጨዋታዎች በአንዱም ያላሸነፈ ሲሆን በአጠቃላይ ሁለቱ ቡድኖች ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ባደረጓቸው ሶስት የማጣሪያ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ሶስቱንም ጨዋታዎች አሸንፋ ሰባት ጎሎችን ተጋጣሚዋ ሱዳን ላይ ስታስቆጥር፤ የተቆጠረባት አንድ ጎል ብቻ ነው።
ባህሬን፤ ዴሞክራሲና እስልምና አንድ ላይ መኖር ይችላሉ?
‘በኢስላማዊ ማኀበረሰብ ዴሞክራሲ ሊኖር ይችላል? ’ዛሬ ይህ ርዕስ በባህሬናውያን ጦማሪዎች መካከል መነጋገሪያ ሆኗል፡፡